አንቺ የሸገር ልጅ እቴ ሸገሬዋ
ፍቅርሽ አሸፈተኝ ተረታሁ ማሬዋ . . .
*
እንደ ወንዜ ጉብል …
ዘርፋፋ ባትለብሺ፣ ሽንሽን ባታሰፊ፤
ሳዱላ ተላጭተሽ፣
ጠጉርሽን ጎንጉነሽ፣ በመስኩ ባታልፊ፤ …
እንሶስላ ሙቀሽ፣
በአልቦ፣ በድሪ፣ በክታብሽ ደምቀሽ፣
ዘንቢልሽን አንቀሽ፣
__ ገበያ ባትሄጂ፤
በአደስ፣ በከርቤ፣
በብርጉዱ ታጥነሽ፣
በጥላሽ ስር ሁነሽ
ጀግናም ባታፋጂ . . . !
*
እኔስ አንቺን አልኩኝ አንቺን ሸገሬዋ
የጣይቱን ሚሞሳ እንቡጧን ማሬዋ . . .*
ሸ- ገ – ሬ – ዋ!
እኔ እንደማውቃት እንደዚያች ኮረዳ…
ውሃ እቀዳ ብለሽ፣
እንስራሽን አዝለሽ፣ ማልደሽ ባትነሺ፤
ባንገትሽ ዝንጉርጉር፣
ጉራማይሌ ጥርስሽ፣ ቀልቤን ባትነሺ፤
ናፍቆቴን ላጋራሽ፣
በምስጢር ባልጠራሽ፣ ፉጨቴን ባትሰሚ፤
ፍቅርሽን ለማግኘት፥
ልብሽን ለማግኘት፣ ባልወረውር ሎሚ . . . !*
በ’ርግጥ አንቺን አልኩኝ አንቺን ሸገሬዋ
የከተማዋን ፈርጥ እንቡጧን ማሬዋ . . .
በአልቦ፣ በድሪ፣ በክታብሽ ደምቀሽ፣
ዘንቢልሽን አንቀሽ፣
__ ገበያ ባትሄጂ፤
በአደስ፣ በከርቤ፣
በብርጉዱ ታጥነሽ፣
በጥላሽ ስር ሁነሽ
ጀግናም ባታፋጂ . . . !
*
እኔስ አንቺን አልኩኝ አንቺን ሸገሬዋ
የጣይቱን ሚሞሳ እንቡጧን ማሬዋ . . .*
ሸ- ገ – ሬ – ዋ!
እኔ እንደማውቃት እንደዚያች ኮረዳ…
ውሃ እቀዳ ብለሽ፣
እንስራሽን አዝለሽ፣ ማልደሽ ባትነሺ፤
ባንገትሽ ዝንጉርጉር፣
ጉራማይሌ ጥርስሽ፣ ቀልቤን ባትነሺ፤
ናፍቆቴን ላጋራሽ፣
በምስጢር ባልጠራሽ፣ ፉጨቴን ባትሰሚ፤
ፍቅርሽን ለማግኘት፥
ልብሽን ለማግኘት፣ ባልወረውር ሎሚ . . . !*
በ’ርግጥ አንቺን አልኩኝ አንቺን ሸገሬዋ
የከተማዋን ፈርጥ እንቡጧን ማሬዋ . . .
*
ሸ- ገ – ሬ – ዋ
እንደዚያች ባተሌ …
አቀበቱን ወጥተሽ፣
ቁልቁለቱን ወርደሽ፣
ማገዶ ባትለቅሚ፣ ከጉድባው ባትፈልጪ፤
ኬሻሽን ዘርግተሽ፣ እህል ባታሰጪ፤
እንክርዳድ ባትለቅሚ፣
ባትከኪ፣ ባትወቅጪ፤
ወገብሽን ጠፍረሽ፣
ወፍጮ ላይ አቀርቅረሽ፣ መጅሽን ባትገፊ፤
ራስሽን ሸብ አ’ርገሽ፣
ጥሬ ባታነፍሺ፣ በወንፊት ባትነፊ፤
ላባወራሽ ክብር
በጭስ ተጨናብሰሽ ቤት ለቤት ባትለፊ::*
መቼም አንቺን አልኩኝ ሁኚኝ እማወራ
አቤት አቤት ልበል ያዘዝሽን ልስራ . . .(አብዲ ሰዒድ
ካዛንቺስ – አዲስ አበባ
ታህሳስ – 2001 E.C)
ሸ- ገ – ሬ – ዋ
እንደዚያች ባተሌ …
አቀበቱን ወጥተሽ፣
ቁልቁለቱን ወርደሽ፣
ማገዶ ባትለቅሚ፣ ከጉድባው ባትፈልጪ፤
ኬሻሽን ዘርግተሽ፣ እህል ባታሰጪ፤
እንክርዳድ ባትለቅሚ፣
ባትከኪ፣ ባትወቅጪ፤
ወገብሽን ጠፍረሽ፣
ወፍጮ ላይ አቀርቅረሽ፣ መጅሽን ባትገፊ፤
ራስሽን ሸብ አ’ርገሽ፣
ጥሬ ባታነፍሺ፣ በወንፊት ባትነፊ፤
ላባወራሽ ክብር
በጭስ ተጨናብሰሽ ቤት ለቤት ባትለፊ::*
መቼም አንቺን አልኩኝ ሁኚኝ እማወራ
አቤት አቤት ልበል ያዘዝሽን ልስራ . . .(አብዲ ሰዒድ
ካዛንቺስ – አዲስ አበባ
ታህሳስ – 2001 E.C)