RSS

“. . . ነፃ አውጪ . . . ”

18 Nov

ከግፍና ከመከራ
__ አገር ነፃ ልታወጣ፣
ፍትህና እኩልነት 
__ በወገን ደጅ ልታሰጣ፣
ድንቁርናን ልታጠፋ፣
የ’ውቀት ብርሃን ልታሰፋ . . . 

ሌት ተቀን የምትዳክር 

__ አንተ ቆራጥ ወገኔ፤
ለውለታህ ቃልም የለኝ 
__ ብርታት ይብዛልህ ወኔ . . . 

*
እቅድ ውጥንህ ተሳክቶ
የልፋትህ ጥግ ፍሬ አፍርቶ
ጨለማችን ለብሶ ትቢያ
ብርሃን ፀዳል ነግሶ ግልቢያ

እንድናየው ባገር ሸንጎ
በደላችን ተጠራርጎ
ጭንቃችንን ተሸክመህ አደባባይ ስትወጣ
ቅንጣት ተስፋችንን ባንደበትህ እንዳናጣ
ከኛ ነፃነት በፊት ነፍስያህን ነፃ አውጣ !!!

(© አብዲ ሰዒድ፣ ሐምሌ 2004 E.C)

 
Leave a comment

Posted by on November 18, 2012 in ግጥም

 

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

 
%d bloggers like this: