በእንትን ጦርነት፣
_ አደጋ ደርሶበት አካሉ የተጎዳ፤
ጠይቋቸው ኖሮ፣
_ የሚታከምበት ገንዘብ እንዲረዳ፤
እነ እንትና ሲመልሱለት …
“በጦርነቱ ወቅት ንጹሃን ሲመቱ፣
ብትመታም ያኔ ቢደርስም ጉዳቱ፣
ለጊዜው ላሁኑ በጀት የተያዘው
ሰለባ የሆኑት የሚታሰቡበት
__ ሐውልት ማሰሪያ ነው።”
___ // አብዲ ሰዒድ // ___
ተጻፈ: 1997 እ. ኢ. አ
መቐለ፣ ኢትዮጵያ
(የኑሮ ቀለም፣ 1998 እ. ኢ. አ)
. . . የሰው ፍቅር ያብዛልን… ለሐውልት ብቻ ሳይሆን ለሰዎች ደህንነትም በጀት የሚይዝ አስተዳደር ያስፋልን …