አንቺ መልከ ብዙ ውበትሽ በዛና
ወዝሽን ሰፈሩት በአሲዳም ቁና።
ዓይንሽን፣ ጥርስሽን፣ ጸጉርሽን እያሉ፣
የአካልሽ ቀበኞች ሰርክ ሲጋደሉ፣
ወይ አንዱ ድል ነስቶ በስስት ሳይዝሽ፣
እንዲሁ በከንቱ ደም ሲፋሰሱብሽ፣
ዘመን መሽቶ ነጋ።
ዘመን መሽቶ ነጋ።
አንቺም ከዘመን ጋር ውበትሽ ረገፈ፣
የሞተልሽ ቀረ፣
የተረፈው ንቆሽ ተራምዶሽ አለፈ።
____ // © አብዲ ሰዒድ // ____
ተጻፈ: 2003 እ. ኢ. አ
ኡፕሳላ፣ ስውዲን።