RSS

የመድረሳ ፍቅር

09 May

(ለሐሊማ)

አሊፍ፣ ባ፣ ታ፣ ሣ . . . *
አሊፍ፣ ባ፣ ታ፣ ሣ . . .
ፊደላት ስንለይ ተቀምጠን መድረሳ
ልሳንና ቀለም ስንመጥን በአበሳ. . .

የኡስታዝን ቁጣ ትንሽ ነፍሴ ፈርታ
ለማሃፈዝ ስጣጣር ሳፋቅድ ስፈታ…

ደግሞ ባንቺ ፍቅር ቀልቤ ሩኋን ስታ
ሰርቄ እያየሁሽ በኩርኩም ስመታ
ያደግኩብሽ ውዴ ናፍቆቴ ሐሊማ
የልጅነት ገዴ ነይ ድምጽሽን ልስማ…

አሊፍ፣ ባ፣ ታ፣ ሣ . . .
አሊፍ፣ ባ፣ ታ፣ ሣ . . .
ኹሩፍ ስንለያይ ተቀምጠን መድረሳ
ልሳንና ቀለም ስንመጥን በአበሳ…

ቁርአኑን ወጣሁት ጨረስኩት ሃፍዤ
አንቺን ለማስደሰት በፍቅርሽ ተይዤ

ታዲያ አሁን ዛሬ ትልቅ ሰው ተብዬ
በትልቆች መሃል በክብር ቁጭ ብዬ
ቁርአኑን ልቀራው በገለጽኩት ቁጥር
ጀነትን ያሳየኝ ቀናው የልጅ ፍቅር
ድቅን እያለብኝ ተቸገርኩ ሐሊማ
ለበይክ አለሁ በይኝ በይ ድምጽሽን ልስማ…

አሊፍ፣ ባ፣ ታ፣ ሣ . . .
አሊፍ፣ ባ፣ ታ፣ ሣ . . .
ፊደላት ስንለይ ተቀምጠን መድረሳ
ልሳንና ቀለም ስንመጥን በአበሳ…

ትዝ ይልሽ እንደሆን ያኔ ልጆች ሳለን
ሐራም ሐላል ሳንል በቅን አብረን ዘለን
አንቺም እጄን ይዘሽ እኔም አንቺን ይዤ
ቁርአኑን ስትወጭው እኔም ባንዴ ሃፍዤ
ቦርቀን ነበረ ለዱንያም ላኼራ
ዛሬ ድምጽሽ ጠፋ በይ ስሚኝ ስጣራ
የኒካው ቀለበት ተቀምጧል በአደራ …

አሊፍ፣ ባ፣ ታ፣ ሣ . . .
አሊፍ፣ ባ፣ ታ፣ ሣ . . .
ፊደላት ስንለይ ተቀምጠን መድረሳ
ልሳንና ቀለም ስንመጥን በአበሳ…

__ // © አብዲ ሰዒድ // __
ተጻፈ: 2004 E.C
ኡፕሳላ፣ ስውዲን።

ማስታወሻ:

ከአረብኛ የተወሰዱና ምናልባት መድረሳ ላልተማረ ሰው ግር ይሉ እንደሁ ብዬ ያሰብኳቸውን ቃላት እንደሚከተለው ትርጓሜያቸውን አስቀምጫለሁ… የተሻለ የአረብኛም ሆነ የመድረሳ ትምህርት እውቀት ያለው ሰው ፍቺዎቹን ቢያሻሽላቸው ደስታዬ ነው…

መድረሳ: የቁርአን ትምህርት ቤት
አሊፍ፣ ባ፣ ታ፣ ሳ፣ . . . የአረብኛ ፍደል ቆጠራ
ኡስታዝ… የቁርአን ወይም የሃይማኖታዊ ትምህርት አስተማሪ
ማሃፈዝ… በቃል ሸምድዶ መያዝ… ወይም በቃል ብቻ መውጣት…
ኹሩፍ… የአረብኛ ፊደል ወይም ፊደል ቆጠራ
ለበይክ … አቤት.. አለሁ እንደማለት
ሐራም… የተከለለ… በሃይማኖት አስተምህሮት የማይፈቀድ
ሐላል… የተፈቀደ… ሊደረግ የሚቻል

 Image

 
3 Comments

Posted by on May 9, 2013 in ግጥም

 

3 responses to “የመድረሳ ፍቅር

  1. tajudin admama

    August 8, 2013 at 8:54 pm

    Betam yamral

     

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

 
%d bloggers like this: