RSS

የራስ ጨዋታ !

02 Aug

ዛፍ ተጥሏል አሉኝ ማዶ ከዚያ መንደር 
ጉዞ ጀምሬያለሁ ማገዶ ልበደር። 
መንደርተኛው ሁሉ መጥረቢያውን ታጥቆ 
ግንድ ይሸነሽናል ሥሩን ሰነጣጥቆ። 

ፍልጡስ ይጠቅመናል ግዴለም ፍለጡ
ግን አደራችሁን ችግኝ አትርገጡ። 
ቡቃያውም ይዟል አምሮበታል ሰብሉ
ምነው ባያረግፉት ወፎች እየበሉ። 
*
ወፍዬ ወፊቱ 
ወፍዬ ወፊቱ
የታደልሽ ፍጥረት ባለጸጋይቱ።

አታርሺ አትዘሪ
ፍቅር ነሽ ስትዞሪ
ማንስ ይከስሻል አገዳ ብትሰብሪ።
*
እኔስ አልዘረጋም፣ ወንጭፌን ጨክኜ
የደም ጎጆ አልሰራም፣ ጠጠር አባክኜ።
ይድላት ትፈንጭበት፣ ያውላት እርሻዬ
የተረፈው ይበቃል፣ አይጠፋም ድርሻዬ
ወፍዬን አትንካት፣ በል ተዋት ባሻዬ።

አንዳንዴ ደግ ነው፣ አንዳንዴም ይከፋል 
የቀበሌው ባሻ፣ ያለማል ያጠፋል። 
ዝንጉርጉር ነው ሆዱ፣ አይለይም መልኩ
ይጠባል ይሰፋል፣ አይታወቅ ልኩ 
ለወፍ ይታጠቃል፣ ጀግና ነው ምትኩ። 
*
ወፍዬ ወፊቷ 
ወፍዬ ወፊቷ
አልጠረጠርሽም ወይ ልበ መልካሚቷ።

ባታርሺ ባትዘሪ 
ፍቅር ብትዘምሪ 
አይተዉሽም እኮ ተይ አትዳፈሪ።

/አብዲ ሰዒድ/
Image

 
Leave a comment

Posted by on August 2, 2013 in ግጥም

 

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

 
%d bloggers like this: