RSS

ያ ሆ… ‘ምቦምቤላ! . . .

17 Jan


በማዲባ ምድር፣ በአቦይ ማንዴላ፣africa cup
በፈርጡ ስቴዲየም፣ በዚያ በ’ምቦምቤላ፣
ያ ሆ በል! ያገር ልጅ፣ በል የ’ርግብ አሞራ፣
ለኩራት ለክብርህ፣ ለእትብትህ ባንዲራ፡፡

ጉሮ ወሸባዬ፣ ጉሮ ወሸባዬ፣ 
ቀና በይ ካንገትሽ፣ እናት ኢትዮጵያዬ፣
ዝናሽ ያንሰራራ፣ ክብርሽ ይድነቃቸው፣
የከርሞ ታሪክሽ፣ ሃይል ይሁን ስንቃቸው፡፡

በቼልፊኮ ጫማ፣ እግር እየደማ፣
በእናት አገር ፍቅር፣ ልብ እየተጠማ፣
ስንት ታሪክ ታየ፣ ስንት ጉድ ተሰማ፡፡ 

ኢታሎ ቫሳሎ፣ ሉችያኖ ቫሳሎ፣
መንግስቱና ግርማ፣ ዝናቸው ከፍ ብሎ፣
ለዘመን ያደረ፣ 
ለአፍ የከበረ፣ ታሪክ እንደጻፉ፣
የዛሬም ልጆችሽ፣ ክብርሽን ያትርፉ፡፡

አዳነ፣ ሳላሃዲን፣ ሳላሃዲን፣ አዳነ፣
አገር ከህመሙ፣ በናንተ እግር ዳነ፣
እንግዲህ ይቅናችሁ፣ ብርታት አይራቃችሁ፣
ሴሌሜ ሴሌሜ፣ በቸር ያድርሳችሁ፡፡

“ሴሌሜ ሴሌሜ፣ ሆ ያ ሴሌሜ፣”
በዋልያ ፍቅር፣ አለሁኝ ታምሜ፤
“ሴላ፣ ሴላ፣ ሴላ፣ 
ሴላላላ ላ ሚያ” 
ድል ካንቺ ጋር ይሁን እናት ኢትዮጵያ፡፡

__________ // __________

© አብዲ ሰዒድ 
ጥር፣ 2005 E.C
shegerewa@gmail.com

 
Leave a comment

Posted by on January 17, 2013 in ግጥም

 

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

 
%d bloggers like this: