RSS

/ ማስታወቂያ ! /

02 Aug

ታላቅ ብለን ያልነው የሰቀልነው ከላይ
ይፈርጥ ጀምሯል እንደበሰለ እንቧይ
ይወርዳል፣ ይዘቅጣል ይሰራል አምቡላ
ማር ጠጅ እንዳልነበር ይሆናል አተላ።

እንደጥሬ እንቁላል ከእጅ እንደወደቀ
አያነሱት ነገር ተጨመላለቀ 
ቦካ ተለወሰ … አካሉ ረከሰ
ገማ በሰበሰ … ሃሳቡ ኮሰሰ።

አድንቀን … አድንቀን 
መርቀን … አፅድቀን 
ሳይቸግር አርቅቀን 
ድንገት አሳቀቀን! 
ኧረ አሸማቀቀን!

ህልማችን መከነ፣ ተስፋችን ተነነ 
ትክን አለ አረረ፣ ውስጣችን በገነ
“ሀ”ብለን ተነሳን፣ ያለፈው ባከነ 
ወየው ታናሽነት !
ወየው ርካሽነት !
‘ወየው… ወየው… ወየው 
እኔስ ስንቱን አየው’ 
ወየው ብለን ቀረን፣ ፀጉራችን በነነ!


… ቃ
….. ጠ
……… ል
……….. ን !

ከንግዲህስ ወዲያ አቋም አውጥተናል!
ላልተወሰነ ቀን፣ 
… ላልተወሰነ ማታ፣
…… ላልተወሰነ ዘመን 

ማድነቅ አቁመናል!
…… ማክበር አቁመናል!
……… አጉል ማሞጋገስ መስቀል አብቅተናል!

መ፟ሸ፟ንገል፣ መ፟ደለል
መ፟ገ፟ፈተር፣ መ፟በደል 
መታሸት፣ መ፟ቀ፟ሸር
መ፟ፈ፟ተግ፣ መበጠር 
መሰጣት፣ መ፟ከካት 
መታመስ፣ መቆላት
መ፟ሰልቀጥ፣ መበላት 
ከንግዲህ በቅቶናል!
ይኸው በአቋምችን ላንዋዥቅ ጸንተናል!

ላልተወሰነ ቀን፣ 
… ላልተወሰነ ማታ፣
…… ላልተወሰነ ዘመን 

ማድነቅ አቁመናል!
…… ማክበር አቁመናል!
……… አጉል ማሞጋገስ ማሽቋለጥ ትተናል!
ይልቅ ለጎጇችን ለራስ በርትተናል!!!

//©አብዲ ሰዒድ //

Image

 
Leave a comment

Posted by on August 2, 2013 in ግጥም

 

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

 
%d bloggers like this: